ዜና | Oduu | News
በልደታ ክፍለ ከተማ ባሉት 10 ወረዳዎች ከተውጣጡ ወጣቶች፣ ሴቶች፣ ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦችና የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች የተሳተፉበት የእንጠያየቅ መድረክ ተካሄደ።

በመድረኩ ሦስት ጽ/ቤት ቤቶች አስተዳደር ፅ/ቤት፣ ንግድ ፣ ሲቪል ምዝገባና የነዋሪዎች አገልግሎትና በተነቡ ሀሳቦች ላይ የጽ/ቤት ሀላፊዎች ምላሽ ሰጥተዋል። የልደታ ክፍለ ከተማ የቤቶች አስተዳደር ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ገመቹ ጌታቸው እንደተናገሩት በአንድ መአከል የአገልግሎትን አሰጣጡን የተሻለና የተቀላጠፈ ለማድረግ የተገልጋዩን ርካታ ያማከለ በቴክኖሎጂና በሰው ኃይልና ስምሪት ፈጣንና ቀልጣፋ በመረጃ የታገዘ አገልግሎት ለመስጠት በቁርጠኝነት ስራዎች እየተሰሩ እንደሆነ ገልፀዋል። የልደታ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ንግድ ጽ/ቤት ወ/ሮ ተስፋነሽ ጋሻው በመድረኩ በተጠየቀው ጥያቄዎች ላይ በሰጡ ሀሳብ እንደገለፁት በቅዳሜና እሁድ አምራችና ሸማቾችን በቀጥታ በማገናኘት ጤናማ ግብይት እንዲኖር በማስቻል ገበያን የማረጋጋት ስራ እየተሠራ መሆኑን ገልፀዋል። መደበኛ ያልሆነ የጎዳና ላይ ንግድ በመደበኛ የንግድ ስርዓት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ የሚያሳርፍ በመሆኑ ወደ ህጋዊ ስርዓት ማምጣት አስፈላጊ እንደሆነ አንስተው መደበኛ ያልሆነ የጎዳና ላይ ንግድ ስራ የሚመራበትን ስርዓት በመዘርጋት የተሰራው ስራ ውጤታማ መሆኑን ገልፀዋል። የልደታ ክፍለ ከተማ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪዎች አገልግሎት ጽ/ቤት ሀላፊ ወ/ሮ መቅደስ ያደታ ዘመናዊ የሲቪልና ቤተሰብ ምዝገባ ስርዓትን ተግባራዊ አድርጎ በመስራት የተማከለ የመረጃ አሰባሰብና አስተዳደር ስርዓት መዝርጋት እንደሚገባ ቀልጣፋ የሆነ አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑን ገልፀዋል። ጽ/ቤቱ የሲቪልና የነዋሪዎችን ምዝገባ ውጤታማነት በማረጋገጥ የማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ልማትን በማቀድና የዜጎችን አገልግሎት ለማሳለጥ ወሳኝ መሆኑን በመድረኩ ወ/ሮ መቅደስ ገልፀዋል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
በልደታ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የቤቶች አስተዳደር ፅ/ቤት ቅዳሜ የውል እድሳት አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።

ተገልጋዮች አገልግሎትን ፈልገው ሲመጡ ፦ ቴሌ ብር ተጠቃሚ መሆንና ክፍያን በዛ መፈፀም፣ የታደሰ የነዋሪነት መታወቂያ ኮፒ፣ የ2017 ዓ.ም ውል፣ ኪራይ የከፈሉበት ደረሰኝ፣ ተወካይ ከሆኑ ህጋዊ ውክልና ኮፒ፣ ወራሽ ከሆኑ የፍርድ ቤት የወራሽነት ማስረጃ ይዘው በመምጣት አገልግሎቱን ማግኘት ይችላሉ።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
የልደታ ክ/ከተማ ቤቶች አስተዳደር ፅ/ቤት የተገልጋዩን እንግልት ለመቀነስ የተለያዩ ዘዴዎችን በመጠቀም ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል።

የክፍለ ከተማው ቤቶች አስተዳደር ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ገመቹ ጌታቸው እንደገለፁት ፅ/ቤቱ በየአመቱ የመንግስት ቤቶች ውል የማደስ ስራ ከዚህ በፊት በየወረዳው ሲሰጥ መቆየቱን ገልፀው በ2018 በጀት ዓመት የወረዳ መዋቅር በመታጠፉ ምክንያት አገልግሎቱ በክፍለ ከተማው እየተሰጠ መሆኑን ገልፀዋል። አቶ ገመቹ አክሎም ተገልጋዮች አገልግሎትን ፈልገው ሲመጡ ፦ ቴሌ ብር ተጠቃሚ መሆንና ክፍያን በዛ መፈፀም፣ የታደሰ የነዋሪነት መታወቂያ ኮፒ፣ የ2017 ዓ.ም ውል፣ ኪራይ የከፈሉበት ደረሰኝ፣ ተወካይ ከሆኑ ህጋዊ ውክልና ኮፒ፣ ወራሽ ከሆኑ የፍርድ ቤት የወራሽነት ማስረጃ ይዘው መምጣት እንዳለባቸው ተናግረዋል ። ፅ/ቤቱ የተገልጋዮች እንግልትና መመላለስ ለማስቀረት የሚያስችለውን ፕሮግራም ያወጣ ሲሆን በዚህ መሰረትም፦ ከጥቅምት 17_23/2018 ዓ.ም ሰኞ ወረዳ 5=30 ቀበሌ ማክሰኞ ወረዳ 3= 26 ቀበሌ ዕሮብ ወረዳ 4=10 ቀበሌ ,ወረዳ 6=12 ቀበሌ,ወረዳ 8=11&12 ቀበሌ ሀሙስ ወረዳ 1=01ቀበሌ,ወረዳ 2=12 ቀበሌ,ወረዳ 10=17ቀበሌ አርብ ወረዳ 9=50ቀበሌ, ወረዳ 7=32ቀበሌ ቅዳሜ ወረዳ 5=43ቀበሌ,ወረዳ 3=36ቀበሌ እሁድ(ጥዋት) ወረዳ 5=42ቀበሌ መሆኑን ተገንዝበው ሁሉም ነዋሪዎች አገልግሎቱን በተቀመጠው መርሀ ግብር ብቻ መስተናገድ እንደሚችሉ ገልፀዋል። ማሳሰቢያ! ፅ/ቤቱ ቀጣይ ያሉትን ፕሮግራሞችን እያሳወቁ እንደምሄዱ ገልፀዋል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
በመኖሪያ ቤት የተፈጠረውን የመልካም አስተዳር ችግር በተመለከተ በቀጣይነት መፍታት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ግለፀኝነት ለመፍጠር ያለመ መድረክ ተካሄደ።

"የነዋሪዎቻችንን የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻል አስተዳደሩ በቁርጠኝነት ይሰራል!" ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ የልደታ ክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ በልደታ ክ/ከተማ አስተዳደር የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመፍታት የሚያስችል የውይይት መድረክ ተካሄደ። መድረኩ በመኖሪያ ቤት የተፈጠረውን የመልካም አስተዳር ችግር በተመለከተ በቀጣይነት መፍታት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ግለፀኝነት ለመፍጠር ያለመ መሆኑን ተገልጿል። የልደታ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ እንደገለጹት የከተማው ብሎም የክ/ከተማው አስተዳደር የከተማዋን ነዎሪዎች የቤት ተጠቃሚ ለማድረግ በሰው ተኮር ስራዎች በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ገልፀው በቀጣይም አጠናክሮ እንደሚቀጥል አንስተዋል። ወ/ሮ ልዕልቲ አክለው እንደገለፁት የመኖሪያ ቤት ችግር ለመፍታት ባለሀብቶችን በማስተባበር፤ እጅግ የተጎሳቀሉና ምቹ ያልሆኑ ቤቶችን በማደስ፤ በሎው ኮስት፣ በኮንደሚኒየም ቁጠባ አማራጭ፣ በማህበር ግንባታ፣ በመንግስትና የግሉ ዘርፍ ትብብር፣ በህገወጥ መንገድ የተያዙ የመንግስት ቤቶችን በማስለቀቅ የቤት ችግሩን ለመፍታት ጥረት እየተደረገ መሆኑን ግንዛቤ አስጨብጠዋል። በክ/ከተማችን በኢኮኖሚ እንዲሁም በአቅም ማነስ መሰረታዊ ፍላጎታቸውን ሳያሟሉ ለችግር የተጋለጡ በርካታ ነዋሪዎች በመዲናዋ መኖራቸውን ገልፀዉ አስተዳደሩ ሰው ተኮር የ90 ቀን ዕቅዶችን በማዘጋጀት ችግሮችን ለመፍታት ርብርብ እያደረገ መሆኑን ወ/ሮ ልዕልቲ ገልፀዋል። ወ/ሮ ልዕልቲ አክለው የነዋሪዎቻችን የቤት ጥያቄዎች ውዝፍ በመሆናቸው ሁሉንም ችግሮችን በአንድ ጊዜ መቅረፍ ባይቻልም ደረጃ በደረጃ እየቀረፍን የነዋሪዎቻችንን የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻል አስተዳደሩ በቁርጠኝነት እየሰራ ነው ብለዋል። አቶ ገመቹ ጌታቸው የክ/ከተማው ቤቶች አስተዳደር ጽ/ቤት ሀላፊ በበኩላቸው የከተማው ውስን ሀብት የሆነው ከመንግስት ቤቶች ባሻገር የመኖሪያ ቤት ችግር ለመቅረፍ ከሚያስችሉት አንዱ የሆነው የጋራ መኖሪያ ቤት ግንባታ ቆጣቢ ነዋሪዎች የከተማ አስተዳደሩ ያዘጋጀውን ይህን አማራጭ ተጠቅመው በማህበር በመደራጀት እና በመቆጠብ የቤት ባለቤት መሆን የሚችሉ መሆኑን ገልፀዋል። የልደታ ክ/ከተማ መልካም አስተዳደር ቅሬታና አቤቱታ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ በላይነህ ሙሉጌታ በመድረኩ ላይ እንዳሉት ከመኖሪያ ቤት ጠያቂዎች ጋር የተደረገው የግንዛቤ መፍጠር ስራ በአጠቃላይ የቤት ማስተላለፍና አስተዳደር በተመለከተ የነበረውን የተዛባ አመለካከት የሚያስተካክል መድረክ መሆኑን ጠቁመዋል። በመጨረሻም የውይይት መድረኩ ከተሳታፊዎች አስተያየት ተሰጥቶበት በመግባባት ተጠናቋል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
ኢትዮጵያ ትችላለች!! በህብረት ችለናል! በአዲስ አበባ ከተማ መስቀል አደባባይ የተካሄደው የድጋፍ ሰልፍ

ኢትዮጵያ ትችላለች!! በህብረት ችለናል! በአዲስ አበባ ከተማ መስቀል አደባባይ የተካሄደው የድጋፍ ሰልፍ የልደታ ክ/ከተማ ነዋሪዎች ተሳትፎ (በፎቶ)፤

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
“ለኢትዮጵያ የብሩህ ተስፋ ቀንዲል ለሆነው የሕዳሴ ግድብ በድል መጠናቀቅ እንኳን አደረሳችሁ” ከንቲባ አዳነች አቤቤ

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናቅቆ መመረቁን አስመልክቶ “ኢትዮጵያ ችላለች!” በሚል መሪ በአዲስ አበባ ሕዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ ተካሂዷል። በድጋፍ ሰልፉ ላይ ንግግር ያደረጉት ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ “ለኢትዮጵያ የብሩህ ተስፋ ቀንዲል፣ የታሪካችን እውነተኛ እጥፋት፣ የማንሰራራት ድንቅ መሠረት ለሆነው ለታላቁ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅ ታሪካዊ እና ሕዝባዊ ድል እንኳን አደረሰን፣ እንኳን አደረሳችሁ! ሲሉ የደስታ መልዕክት አስተላልፈዋል። የአዲስ አበባ ሕዝብ ከሕፃን እስከ አዋቂ፣ ከደሃ እስከ ሀብታም፣ ከተማሪ እስከ ምሁር፣ ከሕዝብ እስከ መሪ በአንድ ድምፅ፣ በአንድ አቋም፣ በኅብረብሔራዊ አንድነት በደማቁ ለተጻፈው እና ለማይደበዝዘው ደማቅ አሻራ መቀነታችንን እና ቀበቶአችንን አጥብቀን ከእለት ጉርሳችን በላባችን፣ በደማችን ጭምር የገነባነው የወል ስኬታችን፣ የድል ብስራታችን ለሆነው ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅ በአብሮነት ደስታችንን ለመግለጽ እና ለጀግናው እና ለማይበገረው ሕዝባችን ምስጋና ለማቅረብ በመስቀል አደባባይ ተገናኝተናል ብለዋል። #ኢትዮጵያ ችላለች #GERD #Ethiopia #addisababa

image
image
image
image